የአገር ገጽታን ለመገንባት ብሎም ማኅራዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጦችን ለማስመዝገብ የግል ዘርፉ አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ሲገለጽ፣ በተለይ በሆቴልና ቱሪዝም መስክ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት የሚንታመንበት ዓውደ ርዕይ ሐሙስ ሰኔ 20 ቀን 2011 ዓ.ም. ሰባተኛው ‹‹ሆቴል ሾው አፍሪካ 2011›› የሆቴልና ቱሪዝም ኢንቨስትመንት ዓውደ ርዕይ በተከፈተበት ወቅትም ይህ ሐሳብ ተንጸባርቋል፡፡

‹‹ከመንግሥት በላይ የግል ዘርፉ የአገር ገጽታን መገንባት ይችላል፡፡ ይህም ሲባል መንግሥት የራሱን ፕሮግራም ሲቀርጽ የግል ዘርፉ ደግሞ እምነት እንዲጣልበት ያደርጋል፤›› ሲሉ አቶ ቁምነገር ተከተል የኦዚ ዓለም አቀፍ የሆቴል ፕሮጀክት አማካሪዎች መሥራችና ባለቤት ገልጸዋል፡፡

Read the full article here